አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በጋራ ያዘጋጁት አራተኛው የኢሬቻ ፎረም እና የዋዜማ ዝግጅት በአዲስ አበባ ከተማ ተካሄደ፡፡
በነገው ዕለት ለሚከበረው የኢሬቻ ክብረ በዓል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢሬፈና የሚከናወንበትን ስፍራ ጨምሮ የተለያዩ የእንግዶች መዳረሻዎችን በማፅዳት ለክብረ በዓሉ ዝግጁ ማድረጉን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡