የሀገር ውስጥ ዜና

የኮሮና ወረርሽኝ በኢኮኖሚ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት በመለየት የሚቻለውን ለማድረግ መንግሥት እንቅስቃሴ ጀምሯል – ጠ/ሚ ዐቢይ

By Tibebu Kebede

March 20, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ወረርሽኝ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተጨባጭ ጉዳት ፈጥኖ በመለየት የሚቻለውን ሁሉ ለማድረግ መንግሥት እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት የጤና ባለሙያዎችን አመስግነው፥ “ጀግኖቹ የጤና ባለሙያዎቻችን ሕዝብን ከስቃይ ለመታደግ አያሌ መሥዋዕትነት ከፍለዋል፤ በሁሉም የጦር ግንባሮች ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን ተሰልፈው ለድንበራችን መከበርና ለሉዓላዊነታችን መረጋገጥ ሕይወታቸውን ሰጥተዋል” ብለዋል።