አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ወረርሽኝ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተጨባጭ ጉዳት ፈጥኖ በመለየት የሚቻለውን ሁሉ ለማድረግ መንግሥት እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት የጤና ባለሙያዎችን አመስግነው፥ “ጀግኖቹ የጤና ባለሙያዎቻችን ሕዝብን ከስቃይ ለመታደግ አያሌ መሥዋዕትነት ከፍለዋል፤ በሁሉም የጦር ግንባሮች ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን ተሰልፈው ለድንበራችን መከበርና ለሉዓላዊነታችን መረጋገጥ ሕይወታቸውን ሰጥተዋል” ብለዋል።