የሀገር ውስጥ ዜና

በካናዳና አሜሪካ በሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አደረጃጀቶች ከ110 ሺህ ዶላር በላይ ተሰበሰበ

By Alemayehu Geremew

October 09, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በካናዳና አሜሪካ በሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አደረጃጀቶች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ባዘጋጁት የድጋፍ ማሰባሰቢያ የበይነ-መረብ መርሐ-ግብር ከ110 ሺህ ዶላር በላይ መሰብሰባቸው ተገለጸ፡፡

ድጋፉ የተሰበሰበው ‘ድር ቢያብር አንበሳ ያስር’ በሚል መርህ መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት መረጃ አመላክቷል፡፡

በካናዳ የኢፌዴሪ አምባሳደር ፍጹም አረጋ ÷ ድጋፉ እንዲሰባሰብ ላስተባበሩ የዳያስፖራ አደረጃጀቶች ኢክናስ ካናዳ፣ ፒቱፒ እና ለሌሎች አጋር አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ለተጎጂ ወገኖች ድጋፍ ለማሰባሰብ የተጀመረው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።