አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ 62 ሺህ ችግኞችን ለሦስተኛ ጊዜ ለጅቡቲ አስረከበች።
በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሉት ፥ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን ወደ ጎረቤት ሀገራት ለማስፋት በያዘችው እቅድ መሠረት ነው ወደ ጅቡቲ ችግኞቹን የላከችው።
ምሳሌ በሆነው በዚህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን የማስፋት ስራ፥ እስካሁን ሩብ ሚሊየን ችግኞች ተለግሰዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!