የሀገር ውስጥ ዜና

የ12ኛ ክፍል የ2014 ዓ.ም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ተጠናቀቀ

By ዮሐንስ ደርበው

October 12, 2022

 

የዩኒቨርሲቲውን ግቢ ሳይለቁ  ቀጣይ ፈተናዎችን የወሰዱና ያለፍላጎታቸው አንድ ፈተና ያመለጣቸው ተፈታኞችም በሚቀጥለው ዙር ፈተናው እንደሚሰጣቸው ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

ፈተናውን በፍላጎታቸው ጥለው የወጡ ተፈታኞችን ግን ዳግም የሚሰጠው ፈተና እንደማይመለከታቸው ተጠቁሟል፡፡

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው አደጋ ፈተና ያልወሰዱትም በቀጣይ ይፈተናሉ ተብሏል።

በሁለተኛው ምዕራፍ ለተፈጥሮ ሣይንስ የትምህርት መስክ ተፈታኞች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ጥቅምት 8 ቀን ፣ 2015 መሰጠት እንደሚጀምር ታውቋል።