አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልሉ ያለው የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት በቂ ባለመሆኑ የተጀመረውን ለውጥ በዘላቂነት ለማስቀጠል ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት ሊሠሩ እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ ተናገሩ፡፡
በጋምቤላ ክልል ፍትሐዊ የጤና አገልግሎት ንቅናቄና 11ኛው ክልል አቀፍ የጤና ዘርፍ ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።