የሀገር ውስጥ ዜና

የማጃንግ የተፈጥሮ ደን እንክብካቤ ሊደረግለት እንደሚገባ አቶ ኡሞድ ኡጁሉ አሳሰቡ

By ዮሐንስ ደርበው

October 15, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ተቋም የተመዘገበው የማጃንግ የተፈጥሮ ደን እንክብካቤ ሊደረግለት እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ አሳሰቡ፡፡

በማጃንግ ባዮስፌር ሪዘርቭ ጥበቃ ዙሪያ በሜጢ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡