የሀገር ውስጥ ዜና

የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሣይንስ ተማሪዎች ፈተና መሰጠት ጀመረ

By ዮሐንስ ደርበው

October 18, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ የሚወስዱ የተፈጥሮ ሣይንስ ተፈታኞች ዛሬ ፈተናቸውን መውሰድ ጀምረዋል፡፡

ፈተናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ነው የሚሰጠው፡፡