አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የተመራ ልዑክ በምሥራቅ ሸዋ ዞን አዳሚ ቱሉ ወረዳ በኩታ ገጠም እየለማ ያለን የበቆሎ ማሳ ጎበኘ፡፡
የምሥራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ መስፍን ተሾመ በጉብኝቱ ላይ ባደረጉት ገለጻ÷ ዛሬ ከተጎበኘው በ2 ሺህ 16 ሔክታር ላይ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል 131 ሺህ ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡