አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 9 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል ከአሸባሪው ህወሓት ነጻ በወጡ አካባቢዎች ሰብዓዊ እርዳታ በተሣለጠ መንገድ እንዲደርስ በቂ ዝግጅት መደረጉን ለሰብዓዊ ድጋፍ የተዋቀረው ኮሚቴ አስታወቀ።
የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦትን ለማሳለጥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ፌደራል ፖሊስ እና የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ ገብቷል።