አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አርአያ ለሆኑ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የሚሰጠውን የአቪዬተርስ አፍሪካ ሽልማት ፕሮግራም በለውጥ ፈጣሪዎች ምድብ ተሸለሙ፡፡
በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በተካሄደው 4ኛው የአቪዬተርስ አፍሪካ ሽልማትና እውቅና መድረክ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ በሰጡት የላቀ የስራ አመራር በለውጥ ፈጣሪዎች ምድብ ተሸላሚ መሆናቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡