የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በስልክ ተወያዩ

By Meseret Awoke

October 24, 2022

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከትሩዶ ጋር ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።

በውይይታቸውም የሀገራቱን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን ጠቁመዋል።