አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮ ቴሌኮም “ቴሌ ክላውድ” የተሰኘ ተቋማት የተለያዩ መረጃዎችን የትም መሄድ ሳይጠበቅባቸው በኢትዮ ቴሌኮም ዳታ ቤዝ ላይ የሚያገኙበት አሠራር ይፋ አደረገ፡፡
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት÷ በአገልግሎቱ ተቋማት የዳታ ሴንተር ወይም የመረጃ ማዕከል መገንባት ሳይጠበቅባቸው የፈለጉትን መረጃ ከኢትዮ ቴሌኮም ማግኘት ይችላሉ፡፡