አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ሰዎችን እንቅስቃሴ መገደብ ብቻ ሳይሆን መለየትና መመርመር ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልግ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም አስታወቁ።
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ባስተላለፉት መልእክት፥ የተየለያዩ የዓለም ሀገራት የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭትን ለመግታት ዜጎቻቸው ከቤት እንዳይወጡ የማድረግ እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን ገልፀዋል።