የሀገር ውስጥ ዜና

300 ቶን ምግብ አላማጣ መድረሱን የዓለም ምግብ ድርጅት አስታወቀ

By Feven Bishaw

November 17, 2022

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 300 ቶን ምግብ አላማጣ መድረሱን የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታወቀ፡፡

ድርጅቱ 300 ቶን ስንዴ፣ አተር ክክ እና የአትክልት ዘይት አላማጣ ድርሶ እየተራገፈ መሆኑን ነው ያስታወቀው፡፡

ምግብ ነክ ቁሳቁሱም ለ67 ሺህ ሰዎች እንደሚደርስም ጠቁሟል፡፡