የሀገር ውስጥ ዜና

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ያሰለጠናቸውን 811 ተማሪዎች አስመረቀ

By Shambel Mihret

December 24, 2022

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት በጤና ሳይንስ ያሰለጠናቸውን 811 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ከተመራቂዎች መካከል 351 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ 457ቱ ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው ተብሏል፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ሀሰን ዩሱፍ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ተመራቂዎች በሰለጠኑበት ሙያ ህዝቡን በተነሳሽነትና በቅንነት እንዲያገለግሉም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡