የሀገር ውስጥ ዜና

የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አክሊሉ ታደሰን የሊጉ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

By ዮሐንስ ደርበው

January 02, 2023

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ባካሔደው ስብሰባ አክሊሉ ታደሰ ለቀጣዮቹ 2 ዓመት ከ6 ወራት ሊጉን እንዲመሩ ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

1 ሺህ 200 መራጮች ድምፅ በሰጡበት የምርጫ ሒደት አክሊሉ ታደሰ 802 ድምፅ በማግኘት ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል፡፡

አባንግ ኩሙዳን 624 እንዲሁም ፈዲላ ቢያ አባመጫ 532 ድምፅ በማግኘት ምክትል ፕሬዚዳንቶች ሆነው መመረጣቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!