የሀገር ውስጥ ዜና

ወጋገን ባንክ በኮረም፣ ማይጨውና መኾኒ ቅርንጫፎች ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀመረ

By ዮሐንስ ደርበው

January 06, 2023

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በግጭት ምክንያት አገልግሎት አቋርጠው የነበሩ የወጋገን ባንክ ተጨማሪ ቅርንጫፎች ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀመሩ፡፡

በዚህም በኮረም፣ ማይጨው እና መኾኒ ቅርንጫፎቹ ባንኩ መሠረታዊ አገልግሎት ዳግም መጀመሩን አስታውቋል፡፡

ወጋገን ባንክ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ እስከ አሁን ድረስ በመቀሌ ዲስትሪክት 33 ቅርንጫፎች እና በሽረ ዲስትሪክት ደግሞ በ19 ቅርንጫፎች በአጠቃላይ በ52 ቅርንጫፎቹ ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!