የሀገር ውስጥ ዜና

የገና በዓልን ለማክበር ወደላሊበላ ያቀኑ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች

By Meseret Awoke

January 07, 2023

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የገና በዓልን ለማክበር ወደላሊበላ ያቀኑ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች በአሉ በሚከበርበት ስፍራ ተገኝተዋል።

በስፍራው የተገኙት ከአስር በላይ ሀገራት አምባሳደሮችና የሀገራት ተወካዮች ትናንት ወደላሊበላ ከገቡ በኋላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናቱን መጎብኘታቸውና በዋዜማው አከባበር ላይ መገኘታቸው ይታወሳል።

በታምሩ ከፈለኝ