የሀገር ውስጥ ዜና

በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከሚታዩ አስቸኳይ ጉዳዮች ውስጥ የቤት ውስጥ ጥቃት ክስ አንዱ እንዲሆን መመሪያ ተሰጠ

By Tibebu Kebede

April 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከሚታዩ ጥቂት አስቸኳይ ጉዳዮች ውስጥ የቤት ውስጥ ጥቃት ክስ አንዱ እንዲሆን መመሪያ መሰጠቱን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ገለፁ።

ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ በትዊተር ገፃቸው እንዳስታወቁት፥ የኮሮና ስርጭትን ለመከላከል ህብረተሰቡ በቤት በሚቆይበት ወቅት በቤት ውስጥ የሚፈፀሙ ጥቃቶች ሊጨምሩ እንደሚችሉ በማሰብ መመሪያው የወጣው።