የሀገር ውስጥ ዜና

ምክር ቤቱ ነገ በሚያደርገው ልዩ ስብሰባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ያፀድቃል

By Tibebu Kebede

April 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልዩ ስብሰባውን በነገው እለት ያካሂዳል።

ምክር ቤቱ ልዩ ስብሰባው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ አባላት ለመሰየም የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብም መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።