የሀገር ውስጥ ዜና

የፓኪስታን የኢንቨስትመንትና የንግድ ልዑክ የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪያል ፓርክን እየጎበኘ ነው

By Shambel Mihret

March 07, 2023

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ70 በላይ የፓኪስታን የኢንቨስትመንት እና የንግድ ልዑካን ቡድን የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪያል ፓርክን እየጎበኘ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ÷ለልዑካን ቡድኑ የፓርኩን ወቅታዊ የስራ እንቅስቃሴ በሚመለከት ገለጻ አድርገዋል፡፡

ልዑኩ በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሚኖረው ቆይታ የተለያዩ አምራች ኩባንያዎችን የምርት ሂደትና የስራ እንቅስቃሴ እንደሚጎበኝ የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡