የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ለአዲሱ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

By Meseret Awoke

March 07, 2023

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ ለአዲሱ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በቅርቡ በናይጄሪያ በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ቦላ ቲኑቡ ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

ፕሬዚዳንቷ ፥ ምርጫው በኢትዮጵያ እና በናይጄሪያ መካከል ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየና ጠንካራ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ያገለግላል የሚል እምነት እንዳላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!