አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጉዞ ታሪክ ያላቸው ዜጎችን በማፈላለግ ከጤና ተቋማት ጋር የማገናኘት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለፁ።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ምላሽ አሰጣጥን በተመለከተ በማህበራዊ ትስስር ድረ ገፆች ለቀረቡላቸው ከ2 ሺህ 500 በላይ ጥያቄዎች በፌስቡክ ገፃቸው በቀጥታ ቀርበው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።