የሀገር ውስጥ ዜና

የጉዞ ታሪክ ያላቸው ዜጎችን በማፈላለግ ከጤና ተቋማት ጋር የማገናኘት ስራ እየተከናወነ ነው- ጤና ሚኒስቴር

By Tibebu Kebede

April 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጉዞ ታሪክ ያላቸው ዜጎችን በማፈላለግ ከጤና ተቋማት ጋር የማገናኘት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለፁ።

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ምላሽ አሰጣጥን በተመለከተ በማህበራዊ ትስስር ድረ ገፆች ለቀረቡላቸው ከ2 ሺህ 500 በላይ ጥያቄዎች በፌስቡክ ገፃቸው በቀጥታ ቀርበው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።