የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል አራት ከተሞች የተጣለው የእንቅስቃሴ እገዳ ማሻሻያ ተደረገበት

By Tibebu Kebede

April 14, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ ክልል አራት ከተሞች ተጥሎ የቆየው የእንቅስቃሴ እገዳ ማሻሻያ እንደተደረገበት የክልሉ ኮሮና ቫይረስ ስርጭት መከላከል ኮማንድ ፖስት አስታወቀ።

በባህር ዳር፣ እንጂባራ፣ ቲሊሊና አዲስ ቅዳም ከተሞች ከመጋቢት 23 2012 ዓ.ም ጀምሮ ተጥሎ የቆየው የተሽከርካሪም ሆነ የሰዎች እንቅስቃሴ ገደብ ከዛሬ ጀምሮ ተነስቷል።