ዓለምአቀፋዊ ዜና

በአፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ15 ሺህ በለጠ

By Tibebu Kebede

April 14, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአፍሪካ አህጉር በኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ15 ሺህ መብለጡ የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።

በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ1 ሚሊየን 900 ሺህ መብለጡን የሚያሳየው የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ፤ ከእነዚህም ውስጥ 15 ሺህ 346 በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ ናቸው።