አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 8፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ተቋርጦ የነበረው የሀገር አቋራጭ፤ አነስተኛ እና መለስተኛ የህዝብ ትራንስፖርት ዛሬ መጀመሩን የትራንስፖርት ባለስልጣን ገለፀ።
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ለመግታት ሲባል የሀገር አቋራጭ የትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡን ያስታወሰው ባለስልጣኑ፥ ከዛሬ ጀምሮ ግን የሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በሚሰጡ ስድስቱም መናኸሪያዎች አገልግሎት መሰጠት መጀመሩን ገልጿል።