የሀገር ውስጥ ዜና

ሚኒስቴሩ ከተመድ የልማት ፕሮግራም ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ተስማማ

By Mikias Ayele

April 17, 2023

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2015(ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስቴር እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (ዩ ኤን ዲ ፒ) ጋር ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡

የፕላንና ልማት ሚኒስቴር  እና  ዩ ኤን ዲ ፒ  በጋራ የሚያከናውኗቸውን ተግበራት በተመለከተ ግምገማ አካሂደዋል፡፡

በግምገማ መድረኩ ተቋማቱ የጋራ ጉዳዮቻቸውን አጠናክረው ለማስቀጠል ስምምነት ላይ መድረሳቸውን  የሚኒስቴሩ  መረጃ ያመላክታል፡፡