የሀገር ውስጥ ዜና

ዕጣ የወጣባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች የግንባታ ማጠናቀቂያ ሥራ ለመጨረስ በቅንጅት እየተሠራ ነው

By ዮሐንስ ደርበው

April 24, 2023

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዕጣ የወጣባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች የግንባታ ማጠናቀቂያ ሥራዎች ለመጨረስ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ገለጸ::

የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት በጉዳዩ ላይ በሰጡት መግለጫ ÷ የ20/80 እና 40/60 ዕጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የማጠናቀቅ ሥራ በከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ ነው ብለዋል።

ግንባታቸው ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ የጋራ መኖሪያ ቤቶቹን ለማጠናቀቅ የከተማ አሥተዳደሩ ከራሱ በጀት ወጪ በማድረግ እየሠራ እንደሆነም ነው የተናገሩት።

ዕጣ የወጣላቸው ነዋሪዎች ቤታቸውን እንዲረከቡ ግንባታ የማጠናቀቅ ሥራዎችን በሌሊትም ጭምር እየተሠሩ መሆናቸውን የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም ኮርፖሬሽኑ ነባር ዕጣ የወጣላቸው ነዋሪዎች እስከ ሠኔ 30 ወደ ቤታቸው እንዲገቡ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ፣ የቀበሌ ቤት ይዘው የሚገኙ ዕጣ የወጣላቸው አንዳንድ ነዎሪዎችም ከሰኔ 30 በኋላ የመልቀቅ ግዴታ እንዳለባቸው አስታውቋል፡፡

በአዲሱ ሙሉነህ #Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!