የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው

By Tibebu Kebede

April 21, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ተጨማሪ ሶስት ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።

ሚኒስትሯ በ24 ሰአታት ውስጥ ለ745 ሰዎች ምርመራ ተደርጎ ሶስት ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ብለዋል። ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ውስጥ ሁለቱ ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ አንዱ ደግሞ ቻይናዊ መሆኑም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ አስታውቀዋል።