አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀገርቱ በተለያዩ የጉምሩክ ኬላ ጣቢያዎች ላይ ግምታዊ ዋጋቸው ከ21 ሚሊየን ብር በላይ የሆነ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በአንድ ሳምንት ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ ከተያዙባቸው ቦታዎች መካካል መተማ፣ አዳማ፣ ባህር ዳር፣ ጅግጅጋ፣ ጋላፊ፣ ድሬደዋ፣ ሀረር፣ ሁመራ፣ ቦሌ አየር መንገድ፣ ሞጆ፣ አዋሽ እና ሌሎች የጉምሩክ ኬላ ጣቢያዎች ይገኙበታል።