የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ደስታ ሌዳሞ ከሐዋሳ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያዩ

By Alemayehu Geremew

May 15, 2023

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ከሐዋሳ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ በተያዘው በጀት ዓመት እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አፈፃፀምና በቀጣይ ዓመት ሊሰሩ በታቀዱ ሥራዎችን ላይ መክረዋል፡፡

አቶ ደስታ ÷ አመራሩ የከተማዋ ገቢ እንዲያድግ፣ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሻሻል፣ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እንዲሁም ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ዕቅድ መሰረት እንዲፈጸሙ አሳስበዋል፡፡

ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራ እንዲቆም እና የዋጋ ንረትን ሊያረጋጋ የሚችል ሥራ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ መመሪያ መስጠታቸውንም የርዕሠ-መስተዳድሩ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡