አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኮቪድ-19ን አስመልክቶ ጥናትና ምርምር በማካሔድ ምክረ ሀሳቦችን የሚያቀርብ ልዩ ግብረ-ሀይል አቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።
ግብረ ሀይሉ “ብሔራዊ የኮቪድ-19 ልዩ የጥናትና ምርምር ግብረ ሀይል” ሲሆን፥ በግብረ ሀይሉ ውስጥም የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትን፣ ተቆጣጣሪ አካላትን፣ የሳይንስ ሙያ ማህበራትን እና የሳይንስ ጥናትና ምርምር የሚሰሩ የውጭ ሀገር ድርጅቶች ተካተዋል።