የሀገር ውስጥ ዜና

አየር መንገዱ በቦሌ ክፍለ ከተማ በመጠለያ ውስጥ ለሚገኙ 400 ዜጎች ለ15 ቀናት የምሳ ምገባ ጀመረ

By Tibebu Kebede

April 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ ክፍለ ከተማ በመጠለያ ውስጥ ለሚገኙ 400 ዜጎች ለ15 ቀናት የሚቆይ የምሳ ምገባ መርሃ ግብር አስጀመረ።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም፥ አየር መንገዱ አስቸጋሪ ጊዜን እያሳለፈም ቢሆን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ግን ወድ ኋላ አይልም ብለዋል።