የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ክልል 2 ሺህ 160 የውሃ መሳቢያ ፓምፖችን ለመስኖ ልማት ማህበራት አስረከበ

By Tibebu Kebede

April 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት 2 ሺህ 160 የውሃ መሳቢያ ፓምፖችን ለመስኖ ልማት ማህበራት አስረከበ።

የርክክብ ስነ ስርዓቱ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት በዛሬው እለት በአዲስ አበባ በሚገኘው የርእሰ መስተዳድሩ ጽህፈት ቤት ቅጥር ግቢ ነው የተካሄደው።