አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሚልተን ኢንዱስትሪዎች በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጣና የታሸገ የዓሣ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ያላቸውን ከፍተኛ ፍላጎት ገለፁ።
በጅቡቲ የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ከሚልተን ኢንዱስትሪዎች ባለቤት እና ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ የኢትዮጵያ መንግሥት ተገቢውን ማበረታቻ በመስጠት ይህንን ፕሮጀክት ለማሳለጥ ቁርጠኛ መሆኑን አምባሳደር ብርሃኑ ማረጋገጣቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!