የሀገር ውስጥ ዜና

በወላይታ ዞን ጊዜያዊ የሕዝበ ውሳኔ ድምፅ ውጤት ይፋ ሆነ

By Meseret Awoke

June 20, 2023

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በወላይታ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ጊዜያዊ የሕዝበ ውሳኔ ድምፅ ውጤት ይፋ ሆኗል፡፡

በዚሁ መሰረት በወላይታ ሶዶ ከተማ ጊዜያዊ የሕዝበ ውሳኔ አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ ውጤት ይፋ መሆኑን ከዞኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተመሳሳይ በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማና ዳሞት ጋሌ ወረዳ ጊዜያዊ የሕዝበ ውሳኔ አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ ውጤት ይፋ መሆኑ ተገልጿል፡፡

መራጩም በየመረጠበት ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ጊዜያዊ ውጤቱን እየተመለከተ ነው፡፡

ከቀናት በኋላ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተጠቃለለ ውጤት እንደሚያሳውቅ ይጠበቃል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!