የሀገር ውስጥ ዜና

ቱርክ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከላከያ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ድጋፍ አደረገች

By Tibebu Kebede

April 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቱርክ መንግስት ለኮቪድ -19 ወረርሽኝ መከላከል ተግባር የሚውሉ የተለያዩ ቁሳቁሶችን በዛሬው እለት ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር አስረከበ።

ድጋፉ በዋነኝነት ለኮቪድ 19 በሽታ መከላከያ ተግባር የሚውሉ ሲሆን፥ 280 ካርቶን ወይም 1 ሺህ 700 ኪሎ ግራም የሆነ የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁሶች፣ የኬሚካል ማጽጃዎች፣ የማጽጃ አልባሳት እና ሌሎችም ቁሳቁሶች ይገኝበታል።