የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ ደረጃቸውን ያልጠበቁ ከ33 ሺህ በላይ የፊት ጭንብሎች ተያዙ

By Tibebu Kebede

April 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምንጩ ያልታወቀ እና ደረጃቸውን ያልጠበቁ ከ33 ሺህ በላይ የፊት መሸፈኛ ማስኮች እና 4 ሺህ 452 ሊትር የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር ተያዘ።

የአዲስ አበባ የምግብ፣ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የኮሮና ወረርሽኝ መከሰትን ተከትሎ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ ጤና ተቋማት እና የመድሀኒት መደብሮች ላይ ምልከታ አድርጓል፡፡