አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምንጩ ያልታወቀ እና ደረጃቸውን ያልጠበቁ ከ33 ሺህ በላይ የፊት መሸፈኛ ማስኮች እና 4 ሺህ 452 ሊትር የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር ተያዘ።
የአዲስ አበባ የምግብ፣ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የኮሮና ወረርሽኝ መከሰትን ተከትሎ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ ጤና ተቋማት እና የመድሀኒት መደብሮች ላይ ምልከታ አድርጓል፡፡