የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በኢትዮጵያ የሳዑዲ ዓረቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

By Mikias Ayele

July 03, 2023

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በኢትዮጵያ የሳዑዲ ዓረቢያ አምባሳደር ፋህድ ኦባይድላህ አል-ሁመይድኒን (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸው አምባሳደር ተሾመ የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም እያከናወናቸው የሚገኙ ፕሮግራሞችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በተጨማሪም አስካሁን የተከናወኑ የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ላይ ለአምባሳደሩ ገለጻ ማድረጋቸውን የኤምባሲው  መረጃ ያመላክታል፡፡