አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውቷ አትሌት ያለም ዘርፍ የኋላው ድል ቀንቷታል።
አትሌቷ ርቀቱን 30 ደቂቃ ከ46 ሴኮንድ በመግባት ነው ቀዳሚ ሆና ያጠናቀቀችው።
የ21 አመቷ አትሌት በስፔን ካስቴሎ ዴ ላ ፕላና የ10ኪሎ ሜትር ውድድርን 29 ደቂቃ ከ14 ሴኮንድ በመግባት የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት መሆኗ ይታወሳል።