አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) 1 ሺህ 351 አሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸው ተራ ቀን ውጭ ሲያሽከረክሩ በመገኘታቸው አስፈላጊው እርምጃ እንደተወሰደባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ለማስፈፀም የወጣውን የትራንስፖርት ዘርፍ አፈፃፀም መመሪያ ተከትሎ በተደረገ ቁጥጥር ከተፈቀደላቸው ቀን ውጭ ሲንቀሳቀሱ በተገኙ ኮድ 2 አሸከርካሪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን በኮሚሽኑ የትራፊክ ቁጥጥር መምሪያ የቀጠና ኃላፊ ኮማንደር በኃይሉ ደጀኔ ተናግረዋል።