የሀገር ውስጥ ዜና

በብሄራዊ የተቀናጀ የፍትህ መረጃ ስርዓት ፕሮጀክት አደረጃጀት ላይ ውይይት ተካሄደ

By Tibebu Kebede

May 02, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አመራሮች ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አመራሮች ጋር የብሄራዊ የተቀናጀ የፍትህ መረጃ ስርዓት ፕሮጀክት አደረጃጀትን በተመለከተ ተወያዩ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በፌስቡክ ገፃቸው እንዳስታወቁትም ውይይቱ ፍሬያማ ነበር።

ይህ ፕሮጀክት በኢንፎርማሽን ቴክኖሎጂ ድጋፍ በሃገሪቱ ውስጥ ያሉትን የፍትህ ተቋማት ተግባርና ሀላፊነት በአግባቡ እና በተቀላጠፈ ሁኔታ ተወጥተው ለህብረተሰቡ ውጤታማ፣ ጥራት ያልው፣ ወጪ ቆጣቢና፣ ግልፅኝነትን ማዕከል ያደረገ የፍትህ ስርዓት እንዲሆን ይረዳልም ብለዋል።