የሀገር ውስጥ ዜና

የጦር መሣሪያ ያለው ማንኛውም ተቋም ወይም ግለሰብ የማስመዝገብ ግዴታ አለበት- ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ

By Tibebu Kebede

May 03, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጦር መሣሪያ ያለው ማንኛውም ተቋም ወይም ግለሰብ በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ የማስመዝገብ ግዴታ እንዳለበት የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ።

የጦር መሣሪያን የመያዝ፣ የመግዛትና የመሸጥ ሥርዓቱ በመንግሥት እውቅና ብቻ የሚያደርግ ዓዋጅ ሥራ ላይ ውሏል።