አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የ9 ወራት የስራ እቅድ አፈፃፀም ረፖርት ተጠሪ ተቋማት እና ምድብ ፅህፈት ቤት ሃላፊዎች በተገኙበት በሸራትን አዲስ ሆቴል አቅርቧል።
በአሁኑ ወቅት ዋናው ርብርብ ኮቪድ-19 መከላከል ቢሆንም የተቋማቱ ሀላፊነት ለዜጎች የመብት እና የፍትህ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ጋር ተያይዞ ይህ ስብሰባ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደ መሆኑን የኢፌዴሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።