የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

By ዮሐንስ ደርበው

July 21, 2023

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ የፖሊት ቢሮ አባል እና ከፓርቲው የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ዳይሬክተር ዋንግ ዪ ጋር ተወያዩ።

በውይይታቸው ከቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ የተላከላቸውን መልዕክት መቀበላቸውን አስታውቀዋል።

በዚህ ወቅትም ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ትብብር አጠናክራ ለመቀጠል ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።