የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሕይወታቸውን ላጡ በ’ሌኒንግራድ ጀግኖች ተከላካዮች መታሰቢያ ሐውልት’ የአበባ ጉንጉን አኖሩ

By Shambel Mihret

July 26, 2023

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ሕይወታቸውን ላጡ በ’ሌኒንግራድ ጀግኖች ተከላካዮች መታሰቢያ ሐውልት’ ላይ የአበባ ጉንጉን አኖሩ፡፡

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ሩሲያ-ቅዱስ ፒተርስበርግ ከተማ መግባታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

“ለሰላም ደኅንነትና ልማት” በሚል መሪ ሐሳብ በሚካሄደው ጉባዔ ላይ 49 የአፍሪካ ሀገራት ይሳተፋሉ፡፡

ለሁለት ቀናት የሚቆየው ጉባዔ ዓላማም÷ የሩሲያ-አፍሪካን ትብብር ማሳደግ መሆኑ ተመልክቷል፡፡

በተጨማሪም የአፍሪካ መንግስታትን ሉዓላዊነት ማጠናከር የጉባዔው ዓላማ ስለመሆኑ ተገልጿል፡፡

ከጉባዔው ጎን ለጎንም የሩሲያ እና አፍሪካን ኢኮኖሚያዊ እና ሰብዓዊ ጉዳዮች የሚመለከቱ ፎረሞች ይደረጋሉ ነው የተባለው፡፡