የሀገር ውስጥ ዜና

የጋምቤላ ክልል ም/ቤት ለክልሉ መንግስት የቀረበውን የ5 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

By Amele Demsew

July 29, 2023

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለክልሉ መንግስት ለ2016 ዓ.ም የቀረበውን የ5 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጽድቋል።

ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት ሲያካሄደው የቆየውን አራተኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ አጠናቋል።

ምክር ቤቱ ለአዲሱ በጀት የልማት እና መልካም አስተዳደር እቅድ ማስፈጸሚያ የቀረበለትን 5 ቢሊየን 330 ሚሊየን ብር በጀት አፅድቋል።

ከፀደቀው በጀት መካከል 2 ቢሊየን 367 ሚሊየን ከክልል የተለያዩ የገቢ ምንጮች እንዲሁም ቀሪው 2 ቢሊየን 963 ሚሊየን ብር ደግሞ ከፌደራል መንግስት በድጎማና ሌሎች አማራጮች የሚሸፈን መሆኑ እንደተገለጸ ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!