አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የመስኖ ልማት ኮሚሽን ከሶስት የስራ ተቌራጮች ጋር በ4 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር የካዛ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታና የተንዳሆ ፒ.ሲ. 16 መልሶ ግንባታና ጥገና ስምምነት ተፈራረመ፡፡
ኮሚሽኑ ስምምነቱን የተፈራረው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ፣ከሱር ኮንስትራክሽን ፕ.ኤል.ሲ. እና ከአፋር ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ጋር ነው።