የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ክልል ለሕዝቡ የሚገባውን ልማት ለማቅረብ እየተሰራ ነው ተባለ

By Tamrat Bishaw

August 01, 2023

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሕዝቡ የሚገባውን ልማት ለማቅረብ እየተሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ተስፋዬ ይገዙ ተናገሩ፡፡

አቶ ተስፋዬ ትምህርት ለትውልድ በሚል መሪ ሐሳብ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት የግንባታ ስራ በወላይታ ሶዶ ከተማ አስጀምረዋል፡፡

ሕብረተሰቡን በማሳተፍ የሊንታላ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ግንባታ እስከሚጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡

የወላይታ ሶዶ ከተማ የልማት ግስጋሴን ለማሳለጥ የትምህርት አቅርቦት አስፈላጊ ነው ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!